Sorry, you need to enable JavaScript to visit this website.

osse

Office of the State Superintendent of Education
 

DC Agency Top Menu

-A +A
Bookmark and Share

የDC የትምህርት ክፍያ ድጋፍ እርዳታ (DCTAG)

ፈጣን ማስፈንጠሪያዎች

የ2025-26 DCTAG ማመልከቻ በፌብሩዋሪ 3፣ 2025 ይከፈታል እና እስከ ኦገስት 15፣ 2025፣ በ3 p.m. ክፍት ሆኖ ይቆያል።

DCTAG የተማሪ ብቁነት

ለDCTAG ብቁ የሚሆነው ማን ነው

የDCTAG አመልካቾች የDCTAG የገንዘብ ድጋፍ (ከዓመታዊው የጊዜ ገደብ በፊት) በሚፈልጉበት አመት ማመልከት አለባቸው እና ብቁ እንደሆኑ እንዲታመን ከዚህ በታች ያሉትን ሁሉንም መስፈርቶች ማሟላትአለባቸው፦

  • የ US ዜጋ ወይም ብቁ ዜጋ-ያለመሆን ሁኔታ መኖር፤
  • ብቁ በሆነ የሕዝብ ወይም የግል ኮሌጅ ወይም ዩኒቨርሲቲ ይማሩ፤
  • አመልካቹ መጀመሪያ ኮሌጅ ከመግባቱ በፊት ቢያንስ ለ12 ተከታታይ ወራት የኮሎምቢያ ዲስትሪክት ኗሪ መሆን፣ እና በአመልካቹ የኮሌጅ ማትሪክ ውስጥ የቀጠለ{ህጋዊ ነዋሪነትን } መያዝ (ማሳሰቢያ፥ የጥገኛ ተማሪዎች [እድሜያቸው ከ24 በታች የሆነ] ህጋዊ ነዋሪነት በወላጅ ወይም አሳዳጊ ይረጋገጣል)፤
  • በፌዴራል የተማሪ ብድር ያልተከፈለ ሁኔታ ውስጥ አለመሆን፤
  • የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምሩቅ መሆን ወይም እንደ GED ወይም ብሄራዊ የውጭ ዲፕሎማ ፕሮግራም (NEDP) ባሉ አማራጭ መንገዶች የሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ማረጋገጫ ያገኙ፤
  • በ15 ዓመታት ውስጥ (2010-2025) የDCTAG ሽልማት የመጀመሪያ ዓመት ሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ማረጋገጫ ማግኘት፤
  • እንደ መደበኛ ዲግሪ ፈላጊ ተማሪ፣ ቢያንስ፣ ለግማሽ ጊዜ መሰረት፣ ለመመዝገብ ተቀባይነት ያለው ወይም ለመጀመሪያው የአንደኛ ዲግሪ ላይ እየሰራ ያለ፤
  • የመጀመሪያ ዲግሪ ያላገኙ ወይም ያልተቀበሉ፤
  • ፕሮፌሽናል ወይም የድህረ ምረቃ ደረጃ የዲግሪ እጩ አይደለም (ለምሳሌ የህግ መምህር (ዶክተር) ወይም ሁለተኛ ዲግሪ፤
  • በአጥጋቢ አካዳሚክ ማሻሻል (SAP) መሰረት ምዝገባ በተደረገበት ወይም የተቀባይነት ምዝገባ በተገኘበት ኮሌጅ/ዩኒቨርስቲ እንደተተረጎመ፤
  • በ DCTAG ከፍተኛ የገቢ ጣሪያዎች መሰረት። የገቢ ደረጃን በሽልማት አመት እና በድህረ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመጀመሪያ አመት ለመወሰን፣ እባክዎ ይህንን መመሪያ ይከልሱ፡- የDCTAG ከፍተኛ ገቢ ሰንጠረዥ። ጥያቄዎች ካሉዎት፣ እባክዎን የእርስዎን የDCTAG አማካሪ ያነጋግሩ።

እባክዎ ያስታውሱ፡ የውጭ አገር ጥናት ፕሮግራሞች ለDCTAG የገንዘብ ድጋፍ ብቁ አይደሉም።

ዳራ
DCTAG ከኮሌጅ ጋር ለተያያዙ የኮሎምቢያ ዲስትሪክት ነዋሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ምርጫዎችን ለማስፋት፣ በ1999 በኮሎምቢያ ዲስትሪክት የኮሌጅ ተደራሽነት ህግ፤ PL 106-98 በኮንግረስ የተፈጠረ እና በ በ2002የዲሲ ኮሌጅ ተደራሽነት ማሻሻያ ህግ እና በ2007 የዲሲ ኮሌጅ ተደራሽነት ማሻሻያ ህግ የተሻሻለ ነው።

በአሁኑ ጊዜ፣ የDCTAG ተቀባዮች በ300 በላይ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች ይማራሉ። ኮሌጅዎ ወይም ዩንቨርስቲዎ በDCTAG ውስጥ መሳተፉን ለማወቅ፣ እባክዎ የእኛን የተሳትፎ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች ዝርዝር ይጎብኙ።

የDCTAG ህጋዊ ነዋሪ መስፈርት
ለDCTAG የገንዘብ ድጋፍ ብቁ ለመሆን፣ አመልካቹ በኮሎምቢያ ዲስትሪክት ውስጥ ቢያንስ ለ12 ወራት በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የአንደኛ ዓመት ትምህርት መከታተል ከመጀመሩ በፊት ህጋዊ ነዋሪነትን ማረጋገጥ አለበት። በኮሎምቢያ ዲስትሪክት ውስጥ የሚቀጥሉት የመኖሪያ አመታት የአመልካቹን የገንዘብ ድጋፍ ብቁነት ለማረጋገጥ እንደ አመታዊ የማመልከቻ ሂደት አካል ሆኖ በየዓመቱ ይገመገማል። አንድ ተማሪ ለDCTAG የገንዘብ ድጋፍ ብቁ ሆኖ እንዲቀጥል የኮሎምቢያ ዲስትሪክት ህጋዊ ነዋሪነት ኮሌጅ በሚመዘገብበት ጊዜ ሁሉ መቆየት አለበት። ለበለጠ ዝርዝር የዲሲ ህግ፣ ርዕስ 38፣ ምዕራፍ 27፣ እና የዲሲ ማዘጋጃ ቤት ደንቦች፣ ርዕስ 29፣ ምዕራፍ 70 ይመልከቱ።

በኮሎምቢያ ዲስትሪክት፣ ህጋዊ ነዋሪነት የሚለው ቃል በኮሎምቢያ ዲስትሪክት የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ለመመዝገብ ብቁነትን ለማረጋገጥ አላማዎች ጥቅም ላይ ሲውል “ነዋሪነት” ከሚለው ቃል ጋር ተመሳሳይ ትርጉም አለው። ህጋዊ ነዋሪነት የአንድ ሰው ቋሚ የመኖሪያ ቦታ ተብሎ ይገለጻል። ስለዚህ፣ ከDCTAG ፕሮግራም ብቁነት ጋር ስለሚገናኝ፣ ህጋዊ ነዋሪነት የሁለት ነገሮች ጥምር ነው፦ (1) ትክክለኛ የአሁን መኖሪያ፣ እና (2) በኮሎምቢያ ዲስትሪክት ውስጥ የመቆየት ፍላጎት። የፌደራል ህግ የDCTAG ሽልማቶችን የሚያገኙ አመልካቾች በኮሎምቢያ ዲስትሪክት ውስጥ ህጋዊ ነዋሪ እንዲሆኑ ያስገድዳል። ግለሰቦች የመኖሪያ ቦታን ሳያሳዩ በዲስትሪክቱ ውስጥ የፖስታ ሳጥን ሊያገኙ ስለሚችሉ፣ OSSE የፖስታ ሳጥን ቁጥርን ተቀባይነት ያለው አድራሻ አድርጎ አይመለከተውም።

የአገልግሎት መገኛ አድራሻ፡-

Kenneth McGhee፣ የDCTAG ዳይሬክተር
መገኛ ኢሜይል፡-
[email protected]
ግለሰቡ አድራሻ፣
(202) 481-3946
የግለሰቡ TTY፣
711
የግለሰቡ የወለል #:
አምስተኛ ፎቅ
የአገልግሎት ስፍራ፣
የGIS አድራሻ፣

1050 First Street, NE
ከተማ፦
ዋሺንግተን
ክልል፦
ዲሲ
ዚፕ፥
20002
ተያያዥ ይዘቶች፦

ለተማሪዎች ስኮላርሺፕ እና ስጦታዎች

Service Contact: 
Kenneth McGhee, DCTAG Director
Contact Email: 
Contact Phone: 
(202) 481-3946
Contact TTY: 
711
Contact Suite #: 
Fifth Floor
Service Location: 

1050 First Street, NE

GIS Address: 
1050 First Street, NE
City: 
Washington
State: 
DC
Zip: 
20002